በዳሌ ውስጥ ያሉ ክፍለአካላት ከቦታቸው መውጣት (ፊስቱላ) ምንድን ነው?

«የደረሰባቸውሕመምአንገታቸውንያስደፋቸውታካሚዎቼቀናሲሉእናክብራቸውሲመለስፊታቸውላይየማየውፈገግታእጅግየምረካበትእናከምንምበላይየምደሰትበትየሥራዬአካልነው፡፡ለዚህምስልኢትዮጵያውያንእናቶችበእርግዝና፣በወሊድእናልጅአስተዳደግወቅትደኅንነታቸውእንዲጠበቅሳላደርግሥራየንአላቆምም » 

 ዶ/ር ለታ የሕክምና ዳይሬክተር እና የቀዶ ሕክምና ባለሙያ፤ ሃምሊን ሐረር የፊስቱላ ሆስፒታል

በዳሌ የሚገኝ ክፍለአካል መውጣት (ፊስቱላ) ምንድነው?


በወሊድ ወቅት ለሚፈጠር ፊስቱላ ከሚሰጥ ሕክምና በተጨማሪ በኢትዮጵያ የሃምሊን ፊስቱላ ማዕከል ለተለያዩ በማሕፀን አካባቢ የጤና እክሎች ሕክምና ይሰጣል፡፡ ከእነዚህ አንዱ በዳሌ የሚገኝ ክፍለአካል ከቦታው መውጣት (ፊስቱላ) ነው፡፡

በዳሌ የሚገኝ ክፍለአካል ከቦታው መውጣት የአንዲት ሴት የአኗኗር ዘይቤ ላይ እጅግ ተፅዕኖ የማሳደር አቅም ያለው በማሕፀን አካባቢ የሚፈጠር የጤና እክል ነው፡፡ የሚከሰተውም፤ በዳሌ ውስጥ ከሚገኙ ክፍለአካላት ውስጥ (የሽንት ፊኛ፣ ማሕፀን፣ እና የዓይነምድር ከረጢት) አንዱ ወይም ከአንድ በላይ የሚሆኑት ከቦታቸው ተነቃንቀው ወደ መራቢያ አካል አካባቢ ሲወርዱ እና እብጠት ሲፈጥሩ ነው፡፡

የክፍለአካላቱ ከቦታቸው መነቃነቅ ተከስቶ ሕክምና ሳያገኝ ከቆየ ሁኔታው እየተባባሰ ሊሄድ ይችላል፡፡ አንዳንዴም ሁኔታው እጅግ ብሶ የኩላሊት ሥራ ላይ ጫና በማሳደር፤ ሽንት መሽናት እንዳይቻል ያደርጋል፡፡ ይህ ደግሞ ኩላሊት ላይ ኢንፌክሽን እና ጉዳት ያመጣል፡፡ በዳሌ ውስጥ የሚገኝ ክፍለአካል ከቦታው  መውጣት በሴቶች ሕይወት ላይ እጅግ አስከፊ ተጽዕኖ ሊያመጣ ይችላል፡፡

በኢትዮጵያ ያጋጠመው ተግዳሮት


የክፍለአካላት ከቦታቸው መውጣት (ፊስቱላ) በአጠቃላይ በዓለም ላይ ያሉ ሴቶች ላይ ተፅዕኖ የሚያሳድር ቢሆንም፤ በአፍሪካ ደግሞ የዚህ የጤና እክል ተጠቂ ሴቶች ቁጥር ከፍ ያለ እንዲሁም ሕክምናውን ተደራሽ ማድረግ አዳጋች ነው፡፡

በኢትዮጵያ ከፍ ያለ የወለድ ምጣኔ፣ በልጅነት የሚመጣ እርግዝና፣ በልጅነት ወቅት የተመጠነ ምግብ አለማግኘት፣ የእናቶች እና የሕፃናት ጤና እንክብካቤ አገልግሎት ተደራሽ አለመሆን እንዲሁም ከፍተኛ የሥራ ጫና፤ በዳሌ የሚገኙ ክፍለአካላት ከቦታቸው የመውጣት ምጣኔን ከፍ ሊያደርጉት ይችላሉ፡፡ በጉዳዩ ያለው አነስተኛ ግንዛቤ እና የጤና አገልግሎት ተደራሽ አለመሆን፤ አብዛኞቹ ሴቶች ከዚህ የጤና እክል ጋር ለዓመታት ያለ ሕክምና እንዲቆዩ ይዳርጋቸዋል፡፡

ታካሚዎች አብዛኛውን ጊዜ ወደ በሃምሊን ሆስፒታል የሚመጡት የክፍለአካል መውጣት ሕመማቸው ሥር ሰዶ፤ መድማት፣ ኢንፌክሽን፣ ተደጋጋሚ የሽንት ቱቦ ኢንፌክሽን፣ የቆዳ መግል እና ቁስለት፣ የሽንት ቱቦ መዘጋት እንዲሁም የኩላሊት ሥራ ማቆምን ጨምሮ ሌሎች መዘዞችን ካስከተለ በኋላ ነው፡፡

ፊስቱላ፤ የዳሌ ክፍለአካል መውጣት ሴቶች ላይ እጅግ አስከፊ አካላዊ እና ሥነልቦናዊ ጫና ያመጣል፡፡

ለዳሌ ክፍለአካላት መውጣት የሚኖረው ተስፋ 


በዳሌ ውስጥ ያለ ክፍለአካል መውጣት የተባባሰ ደረጃ ሲደርስ፤ ቀዶ ሕክምናን ጨምሮ የሚሰጥ ሕክምና የአንዲትን ሴት ጤና እና ሕይወት በአስገራሚ ሁኔታ መቀየር ይችላል፡፡

ለእናቶች ጤና የሚሰጠው ትኩረት ቢጨምርም፤ የክፍለአካል መውጣት እክል ላለባቸው ሴቶች የማኅበረሰብ ጤናን ተደራሽ በማድረግ ረገድ የተሠራው ሥራ ትንሽ ነው፡፡ አብዛኞቹ የማሕፀን ሕክምና ባለሙያዎች የዘመነ የቀዶ ሕክምና ሥልጠና እና የግብዓት አቅርቦት ተደራሽ አልሆኑም፡፡ የዳሌ ክፍለአካላት ከቦታው መውጣት በሀገሪቱ በጣም የተለመደ የማህፀን ጤና እክል ሆኗል፡፡

በስድስቱም የሃምሊን ፊስቱላ ሆስፒታሎች ሥር የሰደደ የዳሌ ክፍለአካላት መውጣት እክልን ለማከም ክሂሎት ያላቸው የዩሮጋይኖኮሎጂ ቀዶ ሕክምና ልዩ ባለሙያዎች ይገኛሉ፡፡ ይህ ሕይወት ቀያሪ የሕክምና አገልግሎት ለታካሚዎች የሚሰጠው በነጻ ነው፡፡ ባለፈው ዓመት ብቻ ሥር የሰደደ የዳሌ ክፍለአካል መውጣት እክልን ለማከም 1477 ቀዶሕክምናዎች በኢትዮጵያ የሃምሊን ፊስቱላ ማዕከል ተካሂደዋል፡፡

የእማማ የሕይወት ታሪክ 


እማማ የ60 ዓመቷ የዕድሜ ባለጸጋ ናቸው፡፡ በሃምሊን ባሕርዳር ፊስቱላ ሆስፒታል ለ10 ዓመታት ያሰቃያቸውን የዳሌ ክፍለአካል መውጣት እክል ለማከም ውጤታማ ቀዶሕክምና ተደርጎላቸዋል፡፡

ታሪካቸውን እንደመከተለው አጫውተውናል፤ «ችግሬን ለሰዎች እንዳላዋይ ኀፍረት ይዞኝ ነበር፤ ባለቤቴን እንኳ ለማማከር አፈርኩ፤ አልጋ ለየሁ እና በራሴ ልጋፈጠው ሞከርኩ፤ ግን ችግሩ ላለፉት 10 ዓመታት በየዕለቱ ጭንቅ ይፈጥርብኝ ነበር፡፡»

እማማ በነጻ ከሃምሊን ያገኙት ቀዶ ሕክምና ሕይወታቸውን እንደቀየረው አስረድተዋል – «ፈውስ ስለሰጣችሁኝ እና መጨረሻዬ ስላማረ፤ የወደፊት ሕይወቴም ስለተስተካከለ ላመሰግናችሁ እወዳለሁ» ብለዋል፡፡